የኢትስዊች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የዓባይ ባንክን 15ኛ ዓመት የምስረታ በዓል አስመልክተው በዓባይ ባንክ ዋናው መሥሪያ ቤት በመገኘት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
የዓባይ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ የኋላ ገሠሠ ከኢትስዊች ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ይለበስ አዲስ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ተቀብለዋል።

አቶ የኋላ ገሠሠ የኢትስዊች ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ይለበስ አዲስ እና የባንኩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ላቀረቡት መልካም ምኞት ምስጋና አቅርበዋል።