ዓባይ ባንክ የታማኝ ግብር ከፋይ የዕውቅና ሽልማት ተበረከተለት Solomon Aynishet October 12, 2024

ዓባይ ባንክ የታማኝ ግብር ከፋይ የዕውቅና ሽልማት ተበረከተለት

photo 2024 10 11 18 26 04

ዓባይ ባንክ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ6ኛ ጊዜ በተዘጋጀው የታማኝ ግብር ከፋዮች የእውቅና እና ሽልማት መርሃግብር ላይ ተሸላሚ ሆነ፡፡

የ6ኛው ዙር የታማኝ ግብር ከፋዮች እውቅና እና ሽልማት ሥነሥርዓት በብሔራዊ ቤተመንግስት ተካሂዷል፡፡

በመርሃግብሩ ላይ 550 ግብር ከፋዮች እውቅና እና ሽልማት ያገኙ ሲሆን፣ ግብር ከፋዮች በሀገር ውስጥ ገቢ በ12 እና በጉምሩክ በ7 የመምረጫ መስፈርቶች መሰረት ተመዝነው እውቅናው ተሰጥቷቸዋል፡፡

የዓባይ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ የኋላ ገሠሠ እውቅና እና ሽልማቱን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ  እጅ ተቀብለዋል ፡፡

Write a comment
Your email address will not be published.