ዓባይ ባንክ ከኢትዮጵያ አይ ቲ ፓርክ ጋር የመግባቢያ ሥምምነት ተፈራረመ Solomon Aynishet April 8, 2026

ዓባይ ባንክ ከኢትዮጵያ አይ ቲ ፓርክ ጋር የመግባቢያ ሥምምነት ተፈራረመ

1

ዓባይ ባንክ ከኢትዮጵያ አይ ቲ ፓርክ ጋር በስትራቴጂያዊ የቢዝነስ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሥምምነት በኢትዮጵያ አይ ቲ ፓርክ ዋና መሥሪያ ቤት ተፈራርመዋል።

የዓባይ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ የኋላ ገሠሠ እና የኢትዮጵያ አይ ቲ ፓርክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ በለጠ እሱባለው የመግባቢያ ሥምምነቱን ተፈራርመዋል፡፡ 

ኃፊዎቹ ለሁለቱ ተቋሞች ብቻ ሳይሆን ለአገር ዕድገት በሚጠቅሙ ቁልፍ የፋይናንስ እና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ላይም በትብብር እንደሚሰሩ በመርሐ-ግብሩ  ተናግረዋል።

በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የሁለቱም ተቋማት ከፍተኛ የማኔጅመንት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

ዓባይ – የታላቅነት ምንጭ!