ባንካችን ዓባይ እና የኢትዮጵያ መድን ድርጅት በስትራቴጂያዊ የቢዝነስ ተግባራት ላይ በጋራ መሥራት የሚያስችላቸውን ሥምምነት ዛሬ መጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ተፈራርመዋል።
ተቋማቱን በመወከል የመግባቢያ ሥምምነቱን የፈረሙት የዓባይ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ የኋላ ገሠሠ እና የኢትዮጵያ መድን ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አቤል ታደሠ ለተቋሞቹ እና ለአገር ዕድገት በሚጠቅሙ ጉዳዮች ላይ ሁሉ በትብብር እንደሚሰሩ በመርሐ-ግብሩ ላይ አሳውቀዋል።



ዓባይ – የታላቅነት ምንጭ!